ዳይናሚክ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አ. ማ.
ለዳይሬክተሮች ቦርድ አባልነት እጩ በመሆን የሚጠቆሙ ግለሰቦች/ድርጅቶች በንግድ ህጉ፣ በብሔራዊ ባንክ መመሪያ
እና በተቋሙ የመመስረቻ ሰነድ ላይ የተቀመጡትን የሚከተሉትን
የብቃት መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባቸዋል:-
1.
የአክሲዮን ማኅበሩ ባለአክሲዮን
የሆኑ፤
2.
የአክሲዮን ማኅበሩ የዳይሬክቶች ቦርድ አባል ሆነው ለማገልግል
ፈቃደኛ የሆኑ፤
3.
በሌላ የፋይናንስ ተቋም ውስጥ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል ያልሆኑ፤
4.
ከታወቀ ከፍተኛ
የትምህርት ተቋም ቢያንስ ዲፕሎማ ያላቸው፣
5.
ቢያንስ 3 ዓመት
የሥራ ልምድ ያላቸው፣
6.
ዕድሜያቸው ቢያንስ
25 ዓመት የሞላ፤
7.
በስነ-ምግባር
- ታማኝ፤ መልካም ስም ያላቸው እና ኃላፊነት የሚሰማቸው፤
8.
በዕምነት ማጉደል፤
በማጭበርበር፤ በስርቆትና ሌሎች መሰል ወንጀሎች በኢትዮጵያም ሆነ በውጭ አገር ተከሰውያልተፈረደባቸው፤
9.
ለመንግስት ተቆጣጣሪ
አካላት ሆን ብለው የሀሰት መረጃ በማቅረብ ወይም መረጃ በመደበቅ ወንጀል ተከሰው እርምጃ ያልተወሰደባቸው፤
10.
በዳይሬክተርነት፣ በዋና ስራ አስፈፃሚነት፣ በከፍተኛ ስራ አመራርነት ወይም በባለቤትነት የሚመሩት ተቋም ከስሮ በፍ/ቤት
ያልተዘጋ ወይም ከፋይናንስ ተቋማት የተበደሩትን ብድር መክፈል አቅቷቸው ንብረቱ በሀራጅ ያልተሸጠ፣ የተበደሩትን ብድር ወይም ያለባቸውን
የግብር ዕዳ ባለመክፈል በፍ/ቤት ተከሰው በጥፋተኛነት ያልተፈረደባቸው፣
11.
የኩባንያው ቅጥር ሠራተኛ
ያልሆኑ፣
12. የሥራ ዘመናቸውን ያጠናቀቁ ዳይሬክተሮች ለተጨማሪ የሥራ ዘመናት እንደገና ሊመረጡ ይችላሉ፣ በተከታታይ ለሶስተኛ ጊዜና ከዚያ በላይ ለመመረጥ ዳይሬክተሮች ቢያንስ ቢያንስ የጉባዔው ተሳታፊዎችን ¾ኛ (75%) የድምፅ ድጋፍ ማግኘት አለባቸው።